Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስነ-ህዝብ ምክር ቤት የምክክር ጉባዔ እየተካሄደ ነዉ

 

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ያዘጋጀው ክልላዊ የስነ-ህዝብ ምክር ቤት የምክክር ጉባዔ በሆሳዕና ከተማ እየተካሄደ ነዉ።

“የተመጠነ ቤተሰብ ለደስተኛ ኑሮና ለፍትሃዊ ተጠቀሚነት” በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ በሚገኘው ጉባዔ የክልሉን ስነ-ህዝብ በሚመለከት ጥናታዊ የዳሰሳ ጽሑፍ እንዲሁም የስነ-ህዝብ የሰባት ዓመት ፕሮግራም ዕቅድ ሰነዶች ቀርበዉ ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።

በጉባዔው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው እና ሌሎች የክልል፣ የዞንና የልዩ ወረዳ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የምክር ቤቱ አባላትና ባለድርሻ አካላት መገኘታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version