Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በዶዶላ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ12 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በምዕራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ወረዳ ኤዶ ከተማ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የ12 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

አደጋው ሁለት በተቃራኒ መስመር ሲጓዙ ከነበሩ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች አንዱ የአህያ ጋሪን ለማትረፍ ሲሞክር በመጋጨታቸው የተፈጠረ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በተከሰተው አደጋም እስካሁን የ12 ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን÷ በ19 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል ጉዳት መድረሱን የዞኑ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version