አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት በመጠናቀቁ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዐባይ ወንዝ ነበር ተገርቶ ወንዝም ሀይቅም ሆነ፤ ከእንግዲህ በወንዝነቱ ይፈሳል፤ በሀይቅነቱ ኢትዮጵያ ለፈለገችው ልማት ሁሉ ለመዋል እጅ ሰጥቷል ብለዋል።
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ በበኩላቸው የግድቡ የመጀመሪያ ዙር ሙሌት በመጠናቀቁ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ግድቡ በአጭር ጊዜ እንዲሞላ ተፈጥሮም ከእኛ ጋር ሆናለች ነው ያሉት።
ለዚህ ስኬታማነት ትልቅ ተሳትፎ የነበራቸውን አካላት አመስግነዋል።
አቶ ሀይለማሪያም ለአፍሪካ ህብረት እና ለሶስቱ ሀገራት መሪዎች ስኬታማ ውይይት በማድረጋቸው ምስጋና አቅርበዋል።

