Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የፌዴሬሽኑ 28ኛው ጠቅላላ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 28ኛው ጠቅላላ ጉባዔ መካሄድ ጀምሯል።

ጉባዔውን በንግግር የከፈቱት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ÷አትሌቲክስ ኢትዮጵያን በዓለም አደባባይ በማስተዋወቅ ትልቅ ሚና ያለውና ከውድድር በላይ መሆኑን ገልጸዋል።

መንግስት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠውም ነው የተናገሩት፡፡

በጉባዔው የ27ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ቃለ ጉባዔ የፀደቀ ሲሆን÷ የፌዴሬሽኑ ያለፉት አራት ዓመታት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት እየቀረበ ይገኛል።

በወርቅነህ ጋሻሁን

Exit mobile version