አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮ ቴሌኮም በ67 ከተሞች ከፍተኛ ፍጥነት እና አስተማማኝ የዳታ አገልግሎት ለማቅረብ የሚያስችለውን ዘመናዊ የ4ጂ LTE የሞባይል አገልግሎት አስጀመረ፡፡
የ4 ጂ LTE ኔትወርክ ማስፋፊያው በከተሞቹ በማደግ ላይ የሚገኘውን የደንበኞቹን ፍላጎት መሰረት ያደረገ መሆኑን ተቋሙ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል፡፡
በቀጣይም በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች ፍላጎትን መሠረት ያደረገ የቴሌኮም ኔትወርክ እና ዲጂታል መሠረተ-ልማቶችን ማስፋፋቱን እንደሚቀጥል አረጋጧል፡፡