አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የጤና ሚኒስቴር ለወሊድና ድንገተኛ ሕክምና አገልግሎት የሚውሉ 370 አምቡላንሶችን ለክልሎች አስረክቧል።
በርክክብ ሥነ ሥርዓቱ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የክልል ጤና ቢሮዎች ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
አምቡላንሶቹ በወሊድና ድንገተኛ ሕክምና አገልግሎት ዘርፍ የሚስተዋለውን ውስንነት መቅረፍ ያስችላሉ ተብሏል።
በመላኩ ገድፍ