Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ተከበረ

አዲስ አበባ፣ ጥር 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጥምቀት በዓል በአዲስ አበባ ልደታ ማሪያም ካቶሊክ ካቴድራል ቤተክርስቲያን ተከበረ።

በዓሉ የሀይማኖት አባቶች፣ የእምነቱ ተከታዮች ምዕምናንና ሌሎች እንግዶች በተገኙበት በቅዳሴ፣ በፀሎት፣ በዝማሬ፣ በምስጋና እና ሌሎች ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶች ነው በድምቀት የተከበረው።

በዓሉ በመላ ሀገሪቱ ባሉ የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያናት እንደተከበረ መገለፁን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

Exit mobile version