አዲስ አበባ፣ ጥር 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) በሶማሌ ክልል ሸበሊ ከተማ ከ130 ሚሊየን ብር በሚልቅ ወጪ የተገነቡ ቤቶችን ለአቅመ ደካማ ወገኖች አስረከቡ፡፡
ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት÷ ቤቶቹ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተተገበሩ ያሉ ሰው ተኮር ፕሮጀክቶች አካል መሆናቸውን ገልጸዋል።
የመንግሥት ዋና ትኩረት የዜጎችን ሁለንተናዊ ብልፅግና ማረጋገጥ በመሆኑ መሰል ሥራዎች ተጠናክረው መቀጠል አለባቸው ማለታቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡