Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከ2 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ እና ተከታታይ መርሐ-ግብር ሲያስተምራቸው የነበሩ ከ2 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ።

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጉቼ ጉሌ(ዶ/ር) ፥ ትምህርት የሁሉ ነገር ቁልፍ በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው ባለፉት ጊዜያት የሀገርን ሁለተናዊ ለውጥ የሚያስቀጥሉ ተማሪዎችን እያሰለጠነ ይገኛል ብለዋል ።

በቀጣይም ዩኒቨርሲቲው በተሰጠው የትምህርት መስክ እና ተልዕኮ በምርምር እና በማህበረሰብ አገልግሎት የተጣለበትን ኃላፊነት ይወጣል ነው ያሉት ።

በተጨማሪም መቱ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መርሐ-ግብሮች ሲያስተምራቸውን የነበሩ 1 ሺህ 400 ተማሪዎችን በመጀመሪያና እና ሁለተኛ ዲግሪ አስመርቋል።

ከእነዚህም ውስጥ 1 ሺህ 181 የሚሆኑት በመጀመሪያ ዲግሪ እና 226 የሚሆኑት ደግሞ በ2ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ መሆናቸው ተገልጿል።

በኢብራሂም ባዲ

Exit mobile version