Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይዎት አለፈ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ አሥተዳደር 01 ቀበሌ ዳሎቻ ማዞሪያ አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይዎት አለፈ፡፡

አደጋው የተከሰተው ዛሬ ከጠዋቱ 2 ሠዓት ገደማ መሆኑን የዞኑ ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃ አመላክቷል፡፡

ከአዲስ አበባ ወደ ሆሳዕና ሲጓዝ የነበረ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪ በመገልበጡ የተከሰተ አደጋ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡

Exit mobile version