Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት አመራሮች አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከልን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አመራሮችና አባላት እንዲሁም የተለያዩ ሲቪክ ማህበራት ተወካዮች አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከልን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝታቸውም ማዕከሉ ኢትዮጵያን በሚመጥን ደረጃ መሰራቱ እጅግ እንዳስደሰታቸው የፖለቲካ ፓርቲ የጋራ ምክር ቤት አመራሮች ተናግረዋል፡፡፡

በቀጣይም መሰል የሀገርን ገጽታ የሚገነቡ ሥራዎች ላይ ከመንግስት ጎን በመቆም እንደሚሰሩ መግለጻቸውን የከንቲባ ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version