Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በሰቆጣ ከተማ የኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ክልል ዋግ ኸምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ከተማ በአሮሚያ ክልል መንግስት ድጋፍ የተገነባው ኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ተጠናቅቆ ርክክብ ተደርጓል፡፡
ትምህርት ቤቱ በ206 ሚሊየን ብር ወጪ መገንባቱ ነው የተገለጸው፡፡
የኦሮሚያ ክልል የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን ለማጠናከርና ተወዳዳሪ ትውልድ ለመፍጠር በሁሉም ክልሎች የኢፋ ቦሩ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶችን ገንብቶ እያስረከበ እንደሚገኝ ተጠቅሷል፡፡
ይህም ወንድማማችነትን ከማጠናከር ባለፈ የጋራ ብልጽግናን ለማፋጠን እንደሚያስችል መጠቆሙን የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡
Exit mobile version