Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

22ኛው የኢትዮጵያ የባህል ስፖርቶች ውድድር መካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 22ኛው የኢትዮጵያ የባህል ስፖርቶች ውድድር እና 18ኛው የባህል ፌስቲቫል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ መካሄድ ጀምሯል፡፡

ከየካቲት 29 እስከ መጋቢት 7 ቀን 2017 ድረስ የሚካሄደው ይህ መርሐ-ግብር፤ “ባህላዊ ስፖርቶቻችን ለጠንካራ ኅብረ-ብሄራዊ አንድነታችን” በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ ተጀምሯል፡፡

በውድድሩ ከ11 ክልሎችና ሁለት ከተማ አሥተዳደሮች የተወጣጡ 1 ሺህ 386 ስፖርተኞች በ11 ባህላዊ ስፖርቶች ይሳተፋሉ።

በውድድሩ ሕግ እና ደንብ የተዘጋጀለት የአፋር ኮኢሶ የተባለ አዲስ ስፖርታዊ ውድድር ዘንድሮ ይተዋወቃል የተባለ ሲሆን፤ በቀጣይ ዓመት ውድድር ላይ እንደሚካተት ተነግሯል።

በትዝታ ወንድሙ

Exit mobile version