Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት የተዳራደሪ ቡድን ስብሰባ በጄኔቫ መካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 5ኛው የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር የስራ ቡድን አባላት ስብሰባ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ መካሄድ ጀምሯል::

የኢትዮጵያ ዋና ተደራዳሪ ቡድን መሪ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው÷ ኢትዮጵያ ለዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድርድር ዝግጁ መሆኗን በመድረኩ አስረድቻለሁ ብለዋል፡፡

አባል ሀገራት የሁለትዮሽ የንግድ ድርድራቸውን ከወዲሁ እንዲያጠናቅቁ በመድረኩ ጥሪ ማቅረባቸውን ገልጸው÷ በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ከ19 ሀገራት በላይ የድጋፍ መልእክት በማስተላለፍ ኢትዮጵያን ማበረታታቸውን ገልፀዋል፡፡

መድረኩ በጥያቄና መልስ መርሐ-ግብር እስከምሽት እንደሚቀጥልም አመላክተዋል፡፡

Exit mobile version