Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሁለት ተጠባቂ ጨዋታዎች ይካሄዳሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ሲቲ ከክሪስታል ፓላስ እንዲሁም አርሰናል ከብሬንትፎርድ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

ቀን 8 ሰዓት ከ30 በሚደረገው የሳምንቱ የመክፈቻ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ክሪስታል ፓላስን በሜዳው የሚያስተናግደበት ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡

መርሐ ግብሩ ሲቀጥል ቀን 11 ሰዓት ላይ ሶስት ጨዋታዎች የሚደረጉ ሲሆን÷በዚህም ብራይተን ከሌስተር ሲቲ፣ ኖቲንግሃም ፎረስት ከኤቨርተን እንዲሁም ሳውዝሃምፕተን ከአስቶንቪላ ይገናኛሉ፡፡

በቅዳሜ ጨዋታዎች ማጠናቀቂያ ምሽት1 ሰዓት ከ30 ላይ አርሰናል በኤሚሬትስ ስታዲየም ብሬንትፎሮድን የሚያስተናግድ ይሆናል፡፡

Exit mobile version