Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

አርሰናል በበርንማውዝ ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በሜዳው ኤሚሬትስ ስታዲየም በርንማውዝን ያስተናገደው አርሰናል 2 ለ 1 ተሸንፏል፡፡

የበርንማውዝን የማሸነፊያ ግቦች ዲያን ሁጅሰንና ኢቫኒልሰን ሲያስቆጥሩ አርሰናልን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ደግሞ ዲክላን ራይስ ከመረብ አሳርፏል፡፡

ቀደም ብለው በተደረጉ ጨዋታዎች አስቶንቪላ ፉልሃምን 1 ለ 0 እንዲሁም ሌስተር ሲቲ ሳውዝሃምፕተንን 2 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡

በሌላ በኩል ኤቨርተን እና ኢፕስዊች ታውን ያረጉት ጨዋታ 2 ለ 2 በሆ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡

Exit mobile version