Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኢትዮጵያ ቡና አዳማ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 30ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ቡና አዳማ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የኢትዮጵያ ቡናን የማሸነፊያ ግቦች ራምኬል ጀምስ እና አማኑኤል አድማሱ አስቆጥረዋል፡፡

የዛሬው የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥሎ ሲካሄድ÷ ምሽት 12 ሰዓት ፋሲል ከነማ ከኢትዮጵያ
ንግድ ባንክ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

ሊጉን ኢትዮጵያ መድን በ60 ነጥብ ሲመራ÷ ኢትዮጵያ ቡና በ51 ነጥብ ይከተላል፡፡

ወራጅ ቀጣና ላይ መቐለ 70 እንደርታ፣ አዳማ ከተማ፣ ስሑል ሽረ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ተቀምጠዋል፡፡

Exit mobile version