Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ዴቪድ ራያ እና ማትዝ ሰልስ የወርቅ ጓንት አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአርሰናል ግብ ጠባቂ ዴቪድ ራያ እና የኖቲንግሃም ፎረስት ግብ ጠባቂ ማትዝ ሰልስ የ2024/25 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ዘመንን የወርቅ ጓንት በጋራ አሸንፈዋል።

ሁለቱ ግብ ጠባቂዎች በውድድር ዓመቱ 13 ጊዜ መረባቸውን ሳያስደፍሩ በመውጣት ነው የወርቅ ጓንቱን ማሸነፍ የቻሉት።

ከብሬንት ፎርድ በውሰት አርሰናልን በተቀላቀለበት የ2023/24 የውድድር ዘመን የወርቅ ጓንቱን ያሸነፈው ዴቪድ ራያ ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት የወርቅ ጓንቱን ማሸነፍ ችሏል።

እንዲሁም በውድድር ዓመቱ ድንቅ ብቃቱ እያሳየ የሚገኘው የኖቲንግሃም ፎረስት ግብ ጠባቂ ማትዝ ሰልስ የሽልማቱ ተጋሪ ሆኗል።

Exit mobile version