Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ሲዳማ ቡና እና ድሬዳዋ ከተማ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና እና ድሬዳዋ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።

ቀን 9 ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሀቢብ ከማል በፍጹም ቅጣት ምት በ45ኛው ደቂቃ ቀዳሚውን ግብ ለድሬዳዋ ከተማ ሲያስቆጥር÷ ሲዳማ ቡናን አቻ ያደረጋትን ግብ ሀብታሙ ታደሰ በ54ኛው ደቂቃ ማስቆጠር ችሏል።

የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት ወላይታ ድቻ እና ባህር ዳር ከተማ ይገናኛሉ።

Exit mobile version