Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ባህር ዳር ከተማ ወላይታ ድቻን 4 ለ 0 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ባህር ዳር ከተማ ወላይታ ድቻን 4 ለ0 አሸንፏል።

ምሽት 12 ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ወንድወሰን በለጠ በሁለተኛው አጋማሽ ለባህር ዳር ከተማ ሦስት ግቦችን በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርቷል።

በተጨማሪም ቀሪዋን አንድ ግብ ፍፁም አለሙ ከእረፍት በፊት አስቆጥሯል።

በዚሁም ባህር ዳር ከተማ ወላይታ ድቻን 4 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

ቀደም ብሎ ቀን 9 ሰዓት በተካሄደው የሊጉ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና እና ድሬዳዋ ከተማ ተጫውተው 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version