Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በመዲናዋ 44 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የወንዝ ዳርቻ ልማት እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የወንዝነት ባህሪያቸውን ለቀው የነበሩትን የመዲናዋ ወንዞች ከብክለት ለመከላከል 44 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የወንዝ ዳርቻ ልማት እየተከናወነ ነው አለ፡፡

የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ዲዳ ድሪባ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት÷ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና በባለስልጣኑ በተደረጉ ጥናቶች ወንዞቹ የተፈጥሮ መልካቸውን ለቀው ለከፍተኛ ብክለት ተጋልጠዋል፡፡

በዚህም ወንዞችን ከብክለት ለመከላከል 44 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የወንዝ ዳርቻ ልማት እየተከናወነ እንደሆነ ተናግረዋል።

የወንዝ ዳርቻ ልማቱ የህዝብ መዝናኛዎች፣ መጸዳጃ ቤቶች፣ የልጆች መጫወቻዎች፣ የአትሌቶች መለማመጃዎችን እና ፓርኮችን አካቶ እየተገነባ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ ንጋቱ ዳኛቸው በበኩላቸው÷ ወንዞችን ከብክለት ለመጠበቅ የወንዞች ልማትና ብክለት መከላከል ደንብ ወደ ስራ ገብቷል ብለዋል፡፡

ደንቡ ወደ ወንዝ ዳርቻ ልማቱ በካይ ነገሮችን የለቀቁ ግለሰቦች እና ተቋማት ከ2 ሺህ እስከ 1 ሚሊየን ብር ድረስ እንደሚቀጡ ተደንግጓልም ነው ያሉት።

በመሳፍንት እያዩ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version