Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ለመስጠት አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን ለመስጠት አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቅቋል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት፤ ፈተናውን በስኬት ለማጠናቀቅ በቅንጅት እየተሰራ ነው።

በዚህም ከክልል ትምህርት ቢሮዎች፣ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ከጸጥታ አካላት እና ሌሎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የፈተና ጥያቄዎች እና የመሰረተ ልማት ዝግጅት ተጠናቅቋልም ነው ያሉት።

ኩረጃን ለማስቀረትም ፈተናዎች በከፍተኛ ስብጥር እንዲዘጋጁ መደረጉን እና ጠበቅ ያለ ቁጥጥር እንደሚኖር አስታውቀዋል።

በፈተና ወቅት ስልክን ጨምሮ ድምጽና ምስል የሚቀርጹ ኤሌክትሮኒክስ ነገሮችን መያዝ በጥብቅ መከልከሉን ጠቅሰው፤ የተከለከሉትን ነገሮች ይዘው የሚገኙ ተፈታኞች ውጤታቸው እንደሚሰረዝ አስገንዝበዋል።

የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ትምህርት ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑ ይታወቃል።

ለፈተና ከሚቀመጡ ከ608 ሺህ ተማሪዎች ውስጥ 150 ሺህ የሚሆኑትን በበይነ መረብ ለመፈተን የሚያስችል ዝግጅት ተደርጓል።

በአልማዝ መኮንን

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version