Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በግብርና ምርት ዘርፍ የተሰጠው የደላላነት ፈቃድ ተሰረዘ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በግብርና ምርቶች ዘርፍ የተሰጠው የደላላነት ፈቃድ ሙሉ በሙሉ ተሰርዟል አለ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር፡፡

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴዔታ አብዱልሃኪም ሙሉ (ዶ/ር) ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት ÷ በዘርፉ ምንም አይነት እሴት ሳይጨምሩ የንግድ ሥርዓቱን የሚረብሹ በርካታ ደላላዎች አሉ፡፡

ስለሆነም በእህል ምርት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በቁም እንስሳት ዘርፍ የተሰጠው የደላላነት ፈቃድ ሙሉ በሙሉ መሰረዙን ተናግረዋል፡፡

ይህን ተከትሎም ደላላዎች ከገበያው እንዲወጡ መደረጉን ጠቅሰው ÷ ከ3 ሺህ በላይ ደላሎች እና አገናኞች ርምጃ እንደተወሰደባቸውም አስረድተዋል፡፡

በቀጣይ ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ በገበያው የሚስተዋሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት በትኩረት ይሰራል ነው ያሉት ሚኒስትር ዴዔታው፡፡

በተመሳሳይ በሲሚንቶ ገበያ ዘርፍ ነጻ የገበያ ሥርዓት በመዘርጋት የሲሚንቶ ዋጋ ከግማሽ በታች እንዲቀንስ መደረጉን አብራርተዋል፡፡

የሲሚንቶ ግብይት ሥርዓትን ሲረብሹ የነበሩ ደላላዎች ና በተለያዩ አካላት ስም ሲነግዱ የነበሩ ግለሰቦች ከዘርፉ እንዲወጡ መደረጋቸውን አረጋግጠዋል፡፡

በመሳፍንት እያዩ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version