አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ክልል ሰላምን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን የህዝቡን ተጠቃሚነት ሊያረጋግጡ የሚችሉ ሁሉን አቀፍ የልማት ስራዎችን ለማከናወን የአመራሩ ሚና ሊጠናከር ይገባል አሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ።
“አርቆ ማየት አልቆ መስራት” በሚል መሪ ሀሳብ በክልሉ አሻጋሪ ዕድገትና የልማት ዕቅድ ላይ ለክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ለአንድ ሳምንት ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቅቋል።
በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ እንደገለጹት፤ ክልሉ ያለውን እምቅ የመልማት አቅም ወደ ስኬት በመቀየር ህዝቡን የልማቱ ተጠቃሚ ለማድረግ አመራሩ ተግቶ ሊሰራ ይገባል።
ለ25 ዓመታት የሚተገበረው የክልሉ የልማት ዕቅድ ፍኖተ ካርታ ውጤታማ እንዲሆን አመራሩ ግንባር ቀደም ሚናውን መወጣት እንዳለበት ገልጸው፤ ጥራት ያለው ዕቅድ ከማውጣት ጀምሮ ዕቅዱን ለመፈፀም ብቁ ሆኖ መገኘት ይገባል ነው ያሉት።
ሀብት በመፍጠር ህዝቡን ተጠቃሚ ያደረገ ልማትን ማረጋገጥ በየደረጃው ካለው አመራር እንደሚጠበቅ አንስተዋል።
ዕቅዱ ኢትዮጵያ ከምትከተለው ብዝሃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ጋር ተጣጥሞ መዘጋጀቱን ጠቅሰው፤ በጀትን በአግባቡ ለልማት ማዋል እንደሚገባ መጠቆማቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
ኃይል ከሚያባክኑ ትናንሽ ነገሮች በመውጣት በመተጋገዝ ዕቅዱን ለማሳካት ሁላችንም ግንባር ቀደም ሆነን ልንረባረብ ይገባል ሲሉም አሳስበዋል።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!