Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በመዲናዋ የተገነቡ 107 የህዝብ ንጽሕና መጠበቂያ ቤቶች አገልግሎት ጀመሩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማቱን ተከትሎ የተገነቡ 107 የህዝብ ንጽሕና መጠበቂያ ቤቶች አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ የህዝብ መጸዳጃ ቤቶች አስተዳደር ቡድን መሪ ጸዳሉ መሰለው እንዳሉት፤ የኮሪደር ልማቱ ለጽዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።

የኮሪደር ልማቱን ተከትሎ የተገነቡ 107 የህዝብ ንጽህና መጠበቂያ ቤቶች አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን ገልጸው፤ በቅርቡ በርካታ የንጽሕና መጠበቂያ ቤቶች ወደ አገልግሎት እንደሚገቡም ጠቁመዋል።

በተጨማሪም የኮሪደር ልማት በሌለባቸው አካባቢዎች ላይ የጤና ሚኒስቴር ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር የህዝብ ንጽሕና መጠበቂያ ቤቶችን እየገነባ ነው ብለዋል።

በቀጣዩ ዓመትም በቢሮው በኩል 100 የህዝብ የንጽሕና መጠበቂያ ቤቶች እንደሚገነቡ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል።

ማህበረሰቡ በህዝብ ንጽህ መጠበቂያ ቤቶች መጠቀም እንዲችል በተሰራው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ መንገድ ላይ የመጸዳዳት ድርጊት መቀነሱን አንስተዋል።

በመዲናዋ ከዚህ ቀደም በተገነቡ የህዝብ ንጽሕና መጠበቂያ ቤቶች 250 እና በኮሪደር ልማቱ ደግሞ 57 ማህበራት ተደራጅተው እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በመሳፍንት እያዩ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version