Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ወደ ፈተና ማዕከላት እየገቡ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ፈተና ማዕከላት እየገቡ ነው።

ተማሪዎቹ ከሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጠውን ፈተና ለመውሰድ ወደ ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ሚዛን አማን እና ቴፒ ካምፓሶች ፣ ወላይታ ዩኒቨርሲቲ ታርጫ ካምፓስ ወደ ተዘጋጁ ማዕከላት እየገቡ እንደሆነ የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ የሺዋስ ዓለሙ ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል።

በክልሉ የግል ተፈታኝ የሆኑ ከ3 ሺህ በላይ የሆኑ ተማሪዎችን ጨምሮ 19 ሺህ 127 ተማሪዎች ለ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና መዘጋጀታቸውን የገለጹት አቶ የሺዋስ፤ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ የማዘጋጀት ሥራዎች መሰራታቸውን አስታውሰዋል።

በዚህም ፈተናው በኦንላይንና በወረቀት የሚሰጥ በመሆኑ ለተማሪዎች አዲስ እንዳይሆን የተግባር ልምምዶች መደረጋቸውንም ጠቅሰዋል።

ተማሪዎቹ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች በመሄድ የሚፈተኑ በመሆኑ ከመደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን የሥነ ልቦና ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል ብለዋል።

የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ማሳወቁ ይታወሳል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version