አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ (ኢባትሎ) የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር በድሬዳዋ አስተዳደር አከናውኗል፡፡
በተጨማሪም ኢባትሎ በአስተዳደሩ ያስገነባው የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገ ሲሆን÷ የትምህርት መርጃ ቁሳቁስም ድጋፍ ተደርጓል፡፡
የኢባትሎ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር)÷ ተቋሙ የወጪ እና ገቢ ንግድን ከማሳለጥ ባሻገር በተለያዩ ዘርፎች ማህበራዊ ሃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
ባለፉት ሶስት ዓመታት ከ77 ሺህ በላይ ችግኝ በመትከል የተራቆቱ አካባቢዎች መልሰው እንዲያገገሙ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል፡፡
በ38 ሚሊየን ብር ወጪ ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው ት/ቤት ኢባትሎ ማህበራዊ ሃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን በተግባር የሚያሳይ ነው ብለዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ከንቲባ ሀርቢ ቡህ በበኩላቸው÷ ኢባትሎ በድሬዳዋ አስተዳደር እያከናወናቸው ለሚገኙ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች ምስጋና አቅርበዋል።
በተስፋዬ ሃይሉ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook WMCC
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!