Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

አርሰናል ቪክተር ጎከሬሽ ማስፈረሙን ይፋ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል ከብዙ የዝውውር ውጣ ውረድ በኋላ ስዊድናዊውን የፊት መስመር አጥቂ ቪክተር ጎከሬሽ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

የሰሜን ለንደኑ ክለብ ለ27 ዓመቱ ተጫዋች 63 ሚሊየን ዩሮ እንዲሁም እየታየ በሚጨመር 10 ሚሊየን ዩሮ ዋጋ ነው ተጫዋቹን ከስፖርቲንግ ሊዝበን ያስፈረመው፡፡

ባለፈው የውድድር ዓመት ብቻ 54 ግቦችን ያስቆጠረው ጎከሬሽ፤ በመድፈኞቹ ቤት ለአምስት ዓመታት የሚያቆየውን ውል ፈርሟል።

ተጫዋቹ በአርሰናል ቤት ትልቅ ቦታ ያለውን 14 ቁጥር ማልያ የሚለብስ ይሆናል።

ተጫዋቹ ከበርካታ ክለቦች ጥያቄ ሲቀርብለት የነበረ ሲሆን፤ ምርጫው አርሰናል ብቻ እንደሆነ በመግለጽ ወደ ክለቡ ለመዘዋወር ግፊት ሲያደርግ ቆይቷል።

Exit mobile version