Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

2ኛው የተባበሩት መንግሥታት የምግብ ሥርዓት ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 2ኛው የተባበሩት መንግሥታት የምግብ ሥርዓት ጉባኤ የበርካታ ሀገራት መሪዎች በተገኙበት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡

ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ያከናወነቻቸው ተግባራትን በጉባኤው መክፈቻ ላይ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አካፍላለች።

የምግብ ስርዓት ጉባኤው በሐምሌ 2015 ዓ.ም በጣልያን ሮም በተካሄደው የመጀመሪያው የምግብ ስርዓት ጉባኤ ላይ የተገቡ ቃሎች ትግበራ ሂደትን መነሻ በማድረግ የሚካሄድ ነው።

በመንግስታት፣ የምግብ አምራቾች፣ የንግድ ማህበረሰቡና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መካከል ያለውን አጋርነት ማጠናከር ሌላኛው የጉባኤው አጀንዳ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

በጉባኤው ላይ ሀገራት የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽንን አስመልክቶ ያገኟቸውን ስኬቶችና ያጋጠሟቸው ተግዳሮቶች ላይ ሪፖርት ያቀርባሉ።

ለምግብ ስርዓት ሽግግር የፋይናንስ አማራጮችን ማስፋትና የኢንቨስትመንት መጠንን መጨመር በሚቻልበት ሁኔታ ላይም በጉባኤው ይመከራል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version