Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በሲዳማ ክልል ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተከናወኑ ህዝብን ተጠቃሚ ያደረጉ የልማት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ አሉ።

በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የ2017 የአባላት ማጠቃለያ የውይይት መድረክ በሀዋሳ ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ ላይ አቶ ደስታ ሌዳሞ እንዳሉት፤ የክልሉን የመልማት አቅም በመለየት ድህነትን መቀነስ የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል።

በተለይም የእንስሳት ልማት፣ የማህበራዊ አገልግሎት፣ የቱሪዝም ልማት፣ የሌማት ትሩፋት፣ የኮሪደር ልማት፣ የስንዴ ልማት፣ የፍራፍሬና ሌሎችም የግብርና ልማት ስራዎች ተጨባጭ ውጤት ተመዝግቦባቸዋል ብለዋል።

የክልሉን ነባራዊ ሁኔታ በማገናዘብ የተቀረጹ 6 ኢንሼቲቮች እና 68 ፓኬጆች ከክልሉ አልፎ እንደ ሀገር የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ጥሩ ማሳያዎች መሆናቸውን ገልጸዋል።

የተገኙ ውጤቶችን በማስፋት፣ ጉድለቶችን በመሙላትና የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ከዳር በማድረስ ለሀገራዊ የብልፅግና ስኬት በጋራ መትጋት ይገባናል ሲሉ አስገንዝበዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አብረሃም ማርሻሎ በበኩላቸው፤ በፓርቲው ጉባኤ የሰላም ግንባታና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮቸ አጽንኦት ተሰጥቷቸዋል ነው ያሉት።

የክልሉን የኢንቨስትመንትና ቱሪዝም አቅም ማሳደግ ላይ ትኩረት መሰጠቱን መግለጻቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።

ከነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ጋር በተያያዘ የሚነሳውን የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ለመቅረፍ በተወሰደ ርምጃ ለውጥ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ርምጃው በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

የሃሳብ ብዝሃነትን በማክበርና የልማት አንድነትን በማጠናከር የሚስተዋሉ ችግሮችን በዘላቂነት የመፍታትና የማስተካከል ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version