Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ለመዲናዋ ከ50 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመቱ የሕክምና መሳሪያዎች ድጋፍ ተደረጉ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሔኖክ አርጋው ፋውንዴሽን ከ50 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመቱ የተለያዩ የሕክምና መሳሪያዎችና ግብዓቶችን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ድጋፍ አድርጓል፡፡

ድጋፉን የተረከቡት የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንዳሉት ÷ ከዳያስፖራ እስከ ሀገር ቤት ያላቸውን ሃብት የሚያካፍሉ ቸር ልብ ያላቸው እልፍ ዜጎች አሉ።

ባዛሬው ዕለትም በአሜሪካ የሚገኘው ሔኖክ አርጋው ፋውንዴሽን ከ50 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመቱ 133 አይነት የሕክምና መሳሪያዎችና ግብዓቶችን አበርክቶልናል ብለዋል።

መሳሪያዎቹ ለኩላሊት፣ ለተኝቶ ታካሚዎች፣ ለጽኑ እና መደበኛ ሕሙማን ሕክምና አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችሉ ተናግረዋል፡፡

ከንቲባዋ ፋውንዴሽኑ ላደረገው ድጋፍ ምስጋና ማቅረባቸውንም የከተማዋ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!
Exit mobile version