Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ተጨባጭ ለውጦች የተመዘገቡበት የአየር ንብረት ለውጥን የመከላከል ስራ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የሰራቻቸው ስራዎች ተጨባጭ ለውጦች የተመዘገቡባቸው ናቸው አለ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴዔታ ስዩም መኮንን የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል በሚሰራው ስራ ኢትዮጵያ ሚናዋን በአግባቡ እየተወጣች መሆኗን አንስተዋል።
እየተሰሩ ያሉ ስራዎችም ተጨባጭ ለውጥ የታየባቸው በመሆኑ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፋዊ የስበትና ተሞክሮ ማዕከል እየሆነች መምጣቷን ነው የገለጹት።
ኢትዮጵያ በመጭዎቹ ሳምንታት ዓለም አቀፍ ጉባዔዎችን እንደምታዘጋጅ አንስተው÷ ሁለተኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል።
በጉባዔው የኢትዮጵያ ተሞክሮ ለዓለም የሚገለጥበት እና በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ውሳኔ የሚተላለፍበት እንደሆነም አመልክተዋል።
ለጉባዔው ስኬታማነት የግሉ ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
በሰለሞን ይታየው
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook WMCC
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!
Exit mobile version