Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ማንቼስተር ሲቲ የሩበን ዲያዝን ኮንትራት አራዘመ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ሲቲ የተከላካይ ስፍራ ተጫዋቹን ሩበን ዲያዝ ኮንትራት ለተጨማሪ ዓመታት ማራዘሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ሩበን ዲያዝ በአዲሱ ኮንትራት መሰረት በማንቼስተር ሲቲ እስከ ፈረንጆቹ 2029 ድረስ የሚቆይ ይሆናል፡፡

የ28 ዓመቱ ተጫዋች ማንቼስተር ሲቲን ከተቀላቀለ ወዲህ የአውሮፓ ሻምፒየንስ እና የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግን ጨምሮ የተለያዩ ዋንጫዎችን አሳክቷል፡፡

ፖርቹጋላዊው የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ሩበን ዲያዝ በፈረንጆቹ 2020 ከቤኔፊካ ማንቼስተር ሲቲን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡

ዲያዝ ኮንትራቱን ካራዘመ በኋላ ደስተኛ መሆኑን በመግለጽ ለማንቼስተር ሲቲ እና ለክለቡ ደጋፊዎች ክብር እንዳለው ተናግሯል፡፡

በወንድማገኝ ጸጋዬ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version