Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በጋምቤላ ክልል የዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቀሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በጋምቤላ ክልል የዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቀሚነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው አለ የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ።

የቢሮው ኃላፊ አቶ ሯች ባያክ እንዳሉት ÷ በክልሉ በግብርና፣ ማእድን፣ ኢንዱስትሪና ሌሎች ዘርፎች ለዜጎች የሥራ እድል ለመፍጠር ትኩረት ተደርጓል፡፡

በበጀት ዓመቱ በክልሉ ለሥራ እድል ፈጠራ ያሉ ምቹ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በመጠቀም ለ24 ሺህ ዜጎች የሥራ እድል ለመፍጠር በትብብር ይሰራል ብለዋል፡፡

እቅዱን ለማሳካትም ከባለፈው የተገኙት መልካም ተሞክሮዎችን በማስፋትና ውስንነቶች በማረም በቅንጅት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

በክልሉ የሚፈጠሩት የሥራ እድሎች ክህሎትን መሰረት ያደረጉ መሆናቸውንም ነው ኃላፊው ያስረዱት፡፡

በተለይም እንደ ሀገር የተጀመረውን የኮደርስ ስልጠና እንደ ምቹ አጋጣሚ በመጠቀም ለዘርፉ ስኬታማነትና ለክህሎት ግንባታ ሥራ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ጠይቀዋል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version