Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በአሕፈሮም ወረዳ በደረሰ የመኪና አደጋ የ13 ሰዎች ህይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በትግራይ ክልል ማዕከላዊ ዞን አሕፈሮም ወረዳ በደረሰ የመኪና አደጋ የ13 ሰዎች ህይወት አልፏል።

የመኪና አደጋው የደረሰው ዛሬ ንጋት 11፡00 ላይ ሴሮ ቀበሌ ልዩ ስሙ መቐልሕ በሚባል አካባቢ እንደሆነ የወረዳው የጸጥታ እና አስተዳደር ጽህፈት ቤት አስታውቋል።

የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ሻምበል ገ/ትንሳዔ ገ/ገርግስ ለፋና ዲጅታል እንዳሉት፤ አደጋው የደረሰው ከእገላ ወረዳ ወደ እንትጮ ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ላይ ነው።

አውቶቡሱ ከዋናው መንገድ በመውጣት 80 ሜትር ጥልቀት ባለው ገደል ውስጥ በመግባቱ በደረሰ አደጋ የ13 ሰዎች ህይወት ማለፉንም ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች ተሳፋሪዎች ላይ ቀላል እና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል ነው ያሉት።

በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች የሕክምና እርዳታ እያገኙ መሆኑን ገልጸው፤ የአደጋው መንስዔ በመጣራት ላይ ነው ብለዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version