Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ውስጣዊ አንድነትና ኢኮኖሚያዊ አቅምን ማጠናከር ይገባል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የብልፅግና ፓርቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ውስጣዊ አንድነትንና ኢኮኖሚያዊ አቅምን ማጠናከር ይገባል አሉ።

የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) የተመሰረተበትን 30ኛ ዓመት አስመልክቶ “መገናኛ ብዙሃን ለብሔራዊ ጥቅምና ለሰላም” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ አውደ ጥናት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ ‘ሚዲያ ለብሔራዊ ጥቅም’ በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሁፍ ያቀረቡት ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ ሁሉም ዜጋ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም በሁለንተናዊ መንገድ ለማስከበር በአንድነት መረባረብ አለበት።

የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም የሚጎዳ ማንኛውንም እንቅስቃሴ በሀሳብ የበላይነት መሞገትና ማክሸፍም እንደሚገባ ገልጸዋል።

ለዚህም ውስጣዊ አንድነትና ሰላምን በማስጠበቅ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ አቅምን ማጠናከርና የዴሞክራሲ አቅም በመገንባት መረባረብ እንደሚገባ ማብራራታቸውውን ኢዜአ ዘግቧል።

መንግስት የኢትዮጵያን ብልፅግና በሁለንተናዊ መንገድ ለማረጋገጥ በሁሉም መስክ እየሰራ እንደሚገኝ አንስተው፤ መገናኛ ብዙሀን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምን ማስከበር ላይ አጀንዳ ፈጥረው መስራት አለባቸው ብለዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version