አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ የሚካሄዱ ዓለም አቀፍ መድረኮች የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን ለማጠናከር በር ከፋች ናቸው አሉ የፖለቲካ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁራን፡፡
በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እና ተመራማሪ ሙሉጌታ ደበበ (ዶ/ር) እንዳሉት፤ በዓለም አቀፍ ጉባኤዎች ላይ የተለያዩ ሀገራት እና ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች የመገኘት ዕድላቸው ሰፊ ነው።
ይህም ከጉባኤዎች ጎን ለጎን ሀገራት ዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን እንዲያጠናሩ ያግዛል ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ ርዕሰ መዲና አዲስ አበባ የሚካሄዱ አህጉር እና ዓለም አቀፍ መድረኮች የሀገራት ትስስርን እና የዲፕሎማሲውን መስክ ለማጠናከር ትልቅ ዕድል ይፈጥራሉ ያሉት ደግሞ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁር ጥላሁን ሊበን ናቸው።
በኢትዮጵያ የሚካሄዱ መድረኮች የዲፕሎማሲ ግንኙነት በማስፋት ሀገራት ግንኙነታቸውን እንዲያጠናክሩ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥሩ አንስተዋል።
ጉባኤዎቹ የዲፕሎማሲ ግንኙነትን የሚያጠናክሩ እና የሀገርን ገጽታ የሚገነቡ በመሆናቸው ዲፕሎማቶችም ሆኑ ሌሎች አካላት ለዘርፉ ስኬት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ምሁራኑ አስገንዝበዋል፡፡
ጉባኤዎቹ በኢትዮጵያ መካሄዳቸው ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአህጉሪቱም ኩራት እንደሆነ ተናግረዋል።
በስንታየሁ አበበ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!