Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የምስራቅ አፍሪካ ኮሙኒኬሽን ማህበር ጉባዔ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 15ኛው የምስራቅ አፍሪካ ኮሙኒኬሽን ማህበር ዓመታዊ ጉባዔ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡
ጉባዔው “ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ለአፍሪካ ትስስር” በሚል መሪ ሃሳብ ነው በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ የሚገኘው፡፡
በመድረኩ የኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር)፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ሳሙዔል ክፍሌ (ዶ/ር) እና የምስራቅ አፍሪካ ኮሙኒኬሽን ማህበር ፕሬዚዳንት ማርጋሬት ጁኮ (ፕ/ር) ተገኝተዋል፡፡
በተጨማሪም ከአባል ሀገራቱ የተውጣጡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን፣ ጋዜጠኞች፣ ተመራማሪዎች እና አጋር አካላት ተሳትፈዋል፡፡
ለሶስት ቀናት የሚቆየውን ጉባዔ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በትብብር አዘጋጅቶታል፡፡
በመራኦል ከድር
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!
Exit mobile version