Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የቡና ምርትን ለማሳደግ የተሰጠው ትኩረት የላቀ ውጤት እያመጣ ነው – አቶ አዲሱ አረጋ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሰጠው ትኩረት የላቀ ውጤት እያመጣ ነው አሉ።

ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን ገላና ወረዳ በመገኘት በቀርጫንሼ ግሩፕ የለማውን የቡና ተክል ተመልክተዋል።

ከጉብኝታቸው በኋላ በሰጡት ማብራሪያ ለቡና ልማት በመንግስት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸው፤ ይህም የቡና ምርትን በማሳደግ ረገው የላቀ ውጤት እያመጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በቀርጫንሼ ግሩፕ የቡና ልማት የውጤቱ ማሳያ መሆኑን አንስተው፤ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘው ይህ የቡና ልማት የጥራትና ምርታማነት ጥሩ ተሞክሮ የታየበት ነው ብለዋል።

ተመሳሳይ ልማት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ማረጋገጣቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የቀርጫንሼ ግሩፕ ሥራ አስኬያጅ እስራኤል ደገፋ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በመንግስት እየተደረገ ያለው ድጋፍ ለውጤታማነት እንዳበቃቸው እና በጥራትና ምርታማነት ላይ ስኬት መመዝገቡን ተናግረዋል።

በገላና ወረዳ ቡናን ከጥላ ዛፍ ውጭ የማልማት ተግባር ከ750 ሄክታር በላይ በሆነ መሬት ላይ መከናወኑንም ጠቁመዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version