አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2017 (ኤፍ ኤምሲ) የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ የክልላችንን የዳበረ ቅርስ፣ ባህል እና ታሪክ ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር በመደመር ማስቀጠል ይገባል አሉ።
‘ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ’ በሚል መሪ ቃል ጳጉሜን 5 የነገው ቀንን አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት፤ መጪው ጊዜ ከዲጂታል ቴክኖሎጂ ውጭ አይታሰብም ብለዋል።
መሪ ቃሉ የቀጣይ ልማታችን መሣሪያ፣ የወደፊታችን መንገድ እና የህዝባችን አቅም ማዘመኛ እንደሆነ የሚያመላክት መሆኑን ገልጸዋል።
ከመጻኢ ብሩህ ራዕይ፣ አዎንታዊ ለውጥ፣ እድገት፣ ከብሩህ ተስፋ እና ጊዜ አንፃር የሚገለጽ እንደሆነ አንስተው፤ የወደፊቱን አዎንታዊ ዕይታ፣ መነሳሳት እና የተሻለ ጊዜን የሚያመላክት ነው ብለዋል።
ዕለቱን ስናከብር የክልላችንን የዳበረ ቅርስ፣ ባህል እና ታሪክ ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር በመደመር፤ የህዝባችን ተጠቃሚነት አጠናክረን ለማስቀጠል ያለንን ዝግጁነት በማረጋገጥ ይሆናል ነው ያሉት።
በክልሉ የዲጂታል መሠረተ ልማት በማጠናከር፣ የህዝብ አገልግሎቶችን ዲጂታል በማድረግ እና ለወጣቶች የቴክኖሎጂ ክህሎት ስልጠናዎችን በስፋት ለማዳረስ ትኩረት እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል።
መጪው ዓመት በዲጂታል ፈጠራ ታግዘን የነገውን የጋራ ራዕይ የምናሳካበት ጊዜ ልናደርገው ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!