Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕከት÷ ዛሬ ጠዋት የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን በጽሕፈት ቤታችን ተቀብዬ በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ተወያይተናል ብለዋል።

በውይይቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከርና የጋራ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮችን በተመለከት ምክክር ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡

Exit mobile version