Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ቶተንሃም ዌስትሃም ዩናይትድን 3 ለ 0 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አራተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቶተንሃም ዌስትሃም ዩናይትድን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ በዌስትሃም ሜዳ በተደረገ ጨዋታ ፓፔ ሳር፣ ሉካስ ቤርጋቫል እና ሚኪ ቫን ዴ ቬን የቶተንሃምን የድል ጎሎች አስቆጥረዋል፡፡

በጨዋታው የዌስትሃሙ ተከላካይ ቶማስ ሶቼክ ባሳየው ያልተገባ ባህሪ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል፡፡

ቀደም ሲል በተደረጉ ጨዋታዎች አርሰናል፣ ኒውካስል፣ ቦርንማውዝ እና ፉልሃም ተጋጣሚዎቻቸውን ሲያሸንፉ ክሪስታል ፓላስ ከሰንደርላንድ እንዲሁም ኤቨርተን ከአስቶንቪላ ጋር ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት ተለያይተዋል።

Exit mobile version