አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከመስከረም እስከ ኅዳር ባሉት ወራት የወባ በሽታ ስርጭት የሚበዛ በመሆኑ ተጋላጭ አካባቢዎችን በመለየት የመከላከል ሥራ እየተሰራ ይገኛል።
የክልሉ ጤና ቢሮ የወባ መከላከል ፕሮግራም ከፍተኛ ባለሙያ ዶ/ር አንተነህ ካሳዬ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት፤ የወባ በሽታን መከላከል እና መቆጣጠር ትኩረት ተሰጥቶታል።
በዚህም ተጋላጭ አካባቢዎችን በመለየት ማህበረሰቡን ያሳተፈ የወባ በሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በክልሉ ከ1 ሚሊየን በላይ የአልጋ አጎበር ለበሽታው ተጋላጭ ለሆኑ አካባቢዎች ማህበረሰብ መሰራጨቱን ተናግረዋል።
በተጨማሪም የበሽታውን ስርጭት ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ማህበረሰቡ ግንዛቤ እንዲኖረው እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
በኢብራሂም ባዲ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!