አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መመረቁን አስመልክቶ ‘በኅብረት ችለናል’ በሚል መሪ ሐሳብ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፎች እየተካሄዱ ነው።
ሰልፉ ባሕር ዳር ከተማን ጨምሮ በጎንደር፣ ደሴ፣ ደብረ ብርሃን፣ ደብረ ማርቆስ፣ ወልዲያ፣ ሰቆጣ፣ ደብረ ታቦር እና በሌሎች ከተሞች ከማለዳው ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል።
በሰልፉ ላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉ ሲሆን የሕዳሴ ግድብ የብልጽግናችን አሻራ፣ ግድባችን – የመቻል ማሳያ የማንሰራራት ጅማሮ ምልክት፣ የሚደገም ድል፣ የሚጨበጥ ብስራት – ሕዳሴ ግድብ እና ለግድቡ የተባበረ ክንድ ለብልጽግናችን ይተጋል የሚሉ መፈክሮች ተሰምተዋል።
በተጨማሪም ግድባችን በራስ አቅም በአፍሪካዊነት ኩራት የተገነባ እውነት፣ ግድባችን የህብረ ብሔራዊነታችን እና የአንድነታችን መሰረት፣ ግድባችን የመነሳት ደወል ብስራት የኢትዮጵያዊነት ድምቀት የሚሉ እና ሌሎች በግድቡ ግንባታ የተገኙ ድሎችን የሚዘክሩ እና ህብረ ብሔራዊ አንድነትን የሚያጠናክሩ መልዕክቶች ተላልፈዋል።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!