Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በኦሮሚያ ክልል በግብርና ዘርፍ ከ14 ሺህ በላይ ዜጎች ወደ ሥራ ገቡ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል በግብርና እና ግብርና ነክ ዘርፍ ላይ በተደረገ የሥራ ዕድል ፈጠራ ከ14 ሺህ በላይ ዜጎች ወደ ሥራ ገብተዋል፡፡
በክልሉ የሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ ዳይሬክተር አቶ ታከለ ቤኛ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት÷በ2018 በጀት ዓመት በግብርና ዘርፍ በቂ የሥራ እድል ለመፍጠር እየተሰራ ነው፡፡
በዚህ መሰረትም በበጀት ዓመቱ ባለፉት ወራት ከ14 ሺህ በላይ ዜጎች ወደ ሥራ እንዲገቡ መደረጉን አስረድተዋል፡፡
በክልሉ 21 ዞኖች በተለያዩ ቦታዎች ወደ ሥራ ለገቡ ዜጎች የመስሪያ ቦታ፣ የእርሻ ትራክተር፣ የማዳበሪያና ሌሎች ግብዓቶችን ማቅረብ ተችሏል ነው ያሉት፡፡
በዘርፉ ያላቸውን ምርታማነት ለማሳደግ የተሟላ ስልጠና እና የገንዘብ ብድር አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉን ተናግረዋል፡፡
በማኑፋክቸሪንግና በሌሎች ዘርፎች ላይ ለሚሰማሩ ዜጎች የሥራ ዕድል በማመቻቸት ወደ ሥራ እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑንም አብራተዋል፡፡
በታሪክ አዱኛ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!
Exit mobile version