Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ሕዳሴ ግድብ የማንሰራራት ከፍታ መሸጋገሪያ ማማችን ነው – እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ በስኬት መጠናቀቅ ለጀመርነው የማንሰራራት ከፍታ መሸጋገሪያ ማማችን ነው አሉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)።

“በሕብረት ችለናል” በሚል መሪ ሐሳብ ግድቡ በስኬት መጠናቀቅን በማስመልከት በክልል ደረጃ የድጋፍ እና የደስታ መግለጫ ሰልፍ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል።

እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በዚህ በወቅት ባስተላለፉት መልዕክት÷ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያን በጋራ ያሳኩት አኩሪ ፕሮጀክት ነው።

ኢትዮጵያዊያን በሕብረት፣ በይቻላልና በፅናት ለስኬት ያበቁት የዚህ ትውልድ ጥንካሬ ማሳያ ፕሮጀክት መሆኑን አንስተው÷ በተለይም የለውጡ መንግስት የግድቡ ግንባታ ከነበሩበት ውስብስብ ችግሮች በማውጣት ለውጤት አብቅቶታል ብለዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ ስኬት በቀጣይ ለሚከናወኑ ትላልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች መሠረት የጣለና ኢትዮጵያ በሀብቷ የመጠቀም መብቷን በተግባር ያረጋገጠችበት መሆኑን ተናግረዋል።

የክልሉ ሕዝብም ለሕዳሴ ግድብ ግንባታ የሚጠበቅበትን ሁሉ ማድረጉን ገልጸው÷ ሕዝቡ ላደረገው ድጋፍም ምስጋና ማቅረባቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

በሰልፉ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version