Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የሕዳሴ ግድብ ለሕዝብ ጉብኝት ክፍት ሊደረግ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብን ከሰኞ ጀምሮ ምዝገባ በማድረግ መጎብኘት ይቻላል አሉ።

ሚኒስትሯ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቱሪስት መስህቦችን ጎብኝተዋል።

በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ጎብኝዎች ሕዳሴ ግድብን በአንድ ጊዜ 50 በመሆን መጎብኘት ይችላሉ።

ምዝገባው በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል እንደሚሆን ሚኒስትሯ አስታውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ታላቁ የኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ ለጎብኚዎች ክፍት እንደሚሆን መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

በፌቨን ቢሻው

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version