Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ለዜጎች የሚሰጠውን ሰው ተኮር አገልግሎት የሚያሻሽል ነው – አቶ አረጋ ከበደ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት መንግሥት ለዜጎች የሚሰጠውን ሰው ተኮር አገልግሎት በማሻሻል የመንግሥትና ሕዝብ ግንኙነት በእጅጉ የሚያሻሽል ነው አሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ።

የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) እና ሌሎች የፌዴራልና ክልል ከፍተኛ ሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በአማራ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በባሕር ዳር ከተማ ተካሂዷል።

አቶ አረጋ ከበደ በዚህ ወቅት÷ መንግሥት ለሕዝብ አንገብጋቢ የመልካም አስተዳደር ችግር ብሎ ከለያቸው ጉዳዮች ውስጥ አንዱ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ችግር መሆኑን አንስተዋል።

በመሆኑም ማዕከሉ ይህንን አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል ዘመኑን የዋጀ በቴክኖሎጂና የዓለም ማኅበረሰብ ልምድ በመውሰድ የሕዝቡን የአገልግሎት ዘርፎች ወደ አንድ ማዕከል በማምጣትና ቅልጥፍናን በማሳለጥ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ መቋቋሙን ተናግረዋል።

የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን ከባሕር ዳር ቀጥሎ በጎንደር እና ደሴ ከተሞች አገልግሎቱን ለማስጀመር እየተሠራ መሆኑን ጠቁመዋል።

አገልግሎት መጀመሩ ለሕዝቡ ከፍተኛ ጥቅም እንደሚያስገኝላቸውን አንስተው÷ መንግሥት ለዜጎች የሚሰጠውን ሰው ተኮር አገልግሎት በማሻሻል የመንግሥትና ሕዝብ ግንኙነት በእጅጉ የሚያሻሽል እንዲሁም እርካታና ቅቡልነት የሚያረጋግጥ እንደሆነ አመልክተዋል።

በአድማሱ አራጋው

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version