Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በአማራ ክልል የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ክልል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ሥራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።

በማዕከሉ የሥራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) እና ሌሎች የፌዴራልና ክልል ከፍተኛ ሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ 14 ተቋማትን በውስጡ የያዘ ሲሆን÷ 47 አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ በመርሐ ግብሩ ተጠቁሟል።

ማዕከሉ በመንግሥት የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ቅሬታዎችን በመፍታት ቴክኖሎጂ መር የሆነ ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት ለመስጠት በማገዝ እንዲሁም ተጠያቂነትን ለማስፈን እንደሚረዳ ተመላክቷል።

በደሳለኝ ቢራራ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version