Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ውጤታማ ስራዎችን ለማስቀጠል በዕቅድ ላይ የተመሰረቱ ተግባራት ይጠናከራሉ – አቶ ኦርዲን በድሪ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ውጤታማ ስራዎችን ለማስቀጠል በዕቅድ ላይ የተመሰረቱ ተግባራት ይጠናከራሉ አሉ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) ከተመራ ቡድን ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ በክልላዊ ኢኮኖሚያዊ አካውንት፣ በኢትዮጵያ ስታትስቲክስ ልማት፣ በዲጂታል ልማት እቅድ እንዲሁም በመንግስት የልማት ፕሮጀክቶች አመራርና አስተዳደር አተገባበር ላይ ያተኮረ ነው።

አቶ ኦርዲን በድሪ በውይይቱ ላይ እንዳሉት፤ በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ ውጤታማ ስራዎች እንዲቀጥሉ እቅድን መሰረት ያደረጉ ተግባራት ይጠናከራሉ።

ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ከለውጡ ወዲህ የመንግስት ፕሮጀክት የማስተዳደር እና የመፈፀም አቅም አድጓል።

ተወዳዳሪ ኢኮኖሚን ለመገንባት እንደሚሰራ ገልጸው፤ ለዚህም በዲጂታል ልማት፣ በክልላዊ ኢኮኖሚ እና በስታትስቲክስ ልማት የተጀመሩ ስራዎችን እንደሚጠናከሩ አረጋግጠዋል።

በክልሎች የሚፈለገውን ውጤት ለማምጣት አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ በቅንጅት እንደሚሰራ ገልጸዋል።

በተስፋዬ ኃይሉ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

Exit mobile version